Abstract:
ባለፉት 20 ዓመታት መንግስት የጤና መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋቱ የጤና አገልግሎቱን
ተደራሽ ማድረግ ተችሏል በዚህም የህዝቡ የጤና ሁኔታ መሻሻሉን ዓለም አቀፍና አገር አቀፍ
የጥናት ሪፖርቶች ያሳያሉ፡፡
ከሀገራችን የጤና ፖሊሲ አንፃር በየወቅቱ እያደገ ያለውን የጤና አገልግሎት ሽፋን ታሳቢ
ባደረገ ሁኔታ የደም ባንኮችን ቁጥር በመጨመርና የአገልገሎቱን ተደራሽነት ለማስፋት
ባለፉት ጥቂት ዓመታት በርካታ ሥራዎች ቢከናወኑም አሁንም የሀገራችንን የጤናማ ደም
እና የደም ተዋጽኦ አቅርቦትን ከማረጋገጥ አኳያ ረጅም ርቀት መጓዝ ይጠበቅብናል፡፡