Abstract:
የኢትዮጵያ ደም እና ቲሹ ባንክ አገልግሎት በቂ፤ ደህንነቱ የተረጋገጠ እና በወቅቱ
የተዘጋጀ ደም እና የደም ተዋፅኦዎችን እንዲሁም ህብረህዋስ ማሰባሰብ እና
የማስተዳደር አገልግሎቶች ለዜጋው ተደራሽ ለማድረግ ታልሞ የተቋቋመ ተቋም ነው፡፡
አገልግሎቱ አገራዊ ሀብት የሆነው ደም በብሄራዊ ደረጃ በቂ ክምችት መኖሩን
ማረጋገጥ፤ ለክልል ደም ባንኮች ተገቢውን ድጋፍ መስጠት እና በትብብር የመስራት
ኃላፊነትም በመቋቋሚያ ደንቡ ተሰጥቶታል፡፡